በመቅመስና በትክክል በመካፈል መካከል ትልቅ ልዩነት አለ። መቅመስ ማለት ጥቂት ነክሶ ማየት ወይም በምላስ መሞከር ነው፤ መካፈል ግን ከመቅመስ አልፎ መመገብ ማለት ነው። ይህች ትንሽ መጽሐፍ እግዚአብሔርን ከመቅመስ ባለፈ ደረጃ ስለማገልገል የተጻፈች ናት። እግዚአብሔር በአገልግሎት ውስጥ ባዘጋጀላችሁ ታላላቅ ነገሮች እንድትካፈሉ ይፈልጋል።
እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ትቀምሱ ዘንድ ብቻ አይደለም፤ በክርስቶስ መካፈል አለባችሁ። በክርስቶስ መካፈል ማለት በእርሱ ውስጥ በጥልቅ መተከልና ሥር መስደድ ማለት ነው። በታዋቂው ደራሲ ዳግ ሂዋርድ ሚልስ (Dag Heward-Mills) በተጻፈው በዚህ አስደናቂ መጽሐፍ ውስጥ፣ ወደ ጥልቁ ገብታችሁ ተካፋይ የምትሆኑባቸውን ብዙ ነገሮች ታገኛላችሁ። በእግዚአብሔር ነገሮች ተካፋይ መሆን እየቻላችሁ ቀማሾች ብቻ መሆን አያስፈልጋችሁም!

Reviews
There are no reviews yet.