“… በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።” ማቴዎስ 24:14
የምታውቀውን ሕይወት ምን ሊያበቃው ይችላል? በሕይወትህ ውስጥ ያሉት ነገሮች ሁሉ እንዲያበቁ የማድረግ ኃይል ያለው ምንድን ነው? በዚህ ምድር ላይ ያለው የአገልግሎትህ ማብቂያ ምልክት ምን ይሆን? ለቤተ ክርስቲያን መቋጫ የሚሆንባት ምንድን ነው? የሁሉም ነገር መጨረሻ ሞት ነው!
በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ካሉት ገጸ-ባህሪያት መካከል ብዙዎቹ አሳዛኝ ለሆነ መጨረሻ በቅተዋል። ሕይወታቸው ለምን እንደተቋጨ ማወቁ አስፈላጊ ነው። የሰዎች አገልግሎት ለምን ወደ ማብቂያው እንደሚመጣ ማወቅ ጠቃሚ ነው።
በዚህ ገላጭ መጽሐፍ አማካኝነት ኩራት፣ አለመታዘዝ፣ ጥላቻ፣ ጠማማነት፣ ዓመፅ እና አለማክበር ሕይወትህንና አገልግሎትህን ሊያበቁ ከሚችሉ አሳዛኝ ነገሮች መካከል ጥቂቶቹ መሆናቸውን ትረዳለህ።
ከዚህ ጥልቅ ሐሳብ ካለው መጽሐፍ ታላቅ ጥበብን ስትቀበል፣ አገልግሎትህ በዚያው ተመሳሳይ በሆነ አውዳሚ መንገድ ከመጠናቀቅ እንዲድን እመኛለሁ።

Reviews
There are no reviews yet.