• ማናችንም በምድር የተሰጠንን ስራ ሳንጨርሰ በሰማዩ ቤታችን መግባት አንፈልግም። አንዳችንም ስንኳ!እግዚአብሔር ለኛ የሰጠንን ስራ መጨረስ እንፈልጋለን። ይህ መጽሐፍ እንዴት ማጠናቀቅ እንደምትችል ይነግርሃል። ይህ መጽሐፍ በዚያ ቀን ምንም አልጎድለኝም እንዳትል በህይወትህ ውስጥ ለሚያጋጥሙህ መለኮታዊ ወቅቶች እንዴት መመለስ እንዳለብህ ያሳይሃል። ስራህን አጠናቅቀህ እግዚአብሔር “ አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ” ለመባል ያብቃህ!

  • ጥበብን ማዳበር ችሎታን ወይንም ክህሎትን ማዳበር ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር ሞገስ አዋቂ ለሆኑት ትመጣለች ይላል። የአገልግሎትም ሥራ ትልቅ ችሎታን ይጠይቃል። ይህ « የአገልግሎት ጥበብ » በመባል የወጣው አዲስ መጽሐፍ የአገልግሎትን ሥራ መስራት ለሚፈልጉ በጣም አስፈላጊ ነው። ስለ አገልግሎት ትክክለኛና ትክክል ያልሆነ አስተሳሰብ ምን እንደሆነ፣የአገልግሎት ሥራ ምንድን ነው፣ በአገልግሎቱ ሥራ ውስጥ ካንተ የሚጠበቀው ምንድን ነው እና የአገልጋይነቴን ተግባር እንዴት ነው የምወጣው የሚሉትን በማብራራት በግልጽ ያስቀምጠዋል። በአገልግሎት ውስጥ ያንተን ተግባር እንዴት መሥራት እንዳለብህ ያሳስብሃልን? ይህ ልዩ የሆነ የዳግ ሂዋ

  • ዳግ ሂዋርድ ሚልስ በጊዜው አገልግሎት ውስጥ ያለውን የእውነተኛ ህይወት ገጠመኞች በዚህ ድንቅ ስራው ይገመግማል፡፡ ገንዘብ፣ፖለቲካ፣ከተቃራኒ ፆታ ጋር ስለሚኖረን ግንኙነቶችና አገልግሎታዊ ተጽዕኖችን የመሳሰሉትን ጠቃሚ የሆኑ ጉዳዮችን ያሳየናል፡፡ ይህ መጽሐፍ ለእያንዳዱ መሪ ሊኖረው የሚገባ፣ ለጥሪህ መሰረታው የሆኑ ልምምዶችን በቀላሉ የሚያስረዳ መመሪያ ነው፡፡ ለመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና በቤተክርስቲያን ውስጥ ለሚሰሩ እንዲኖራቸው በከፍተኛው የሚመከር ነው።

  • በዚህ ለየት ባለ መጽሐፍ ውስጥ ዳግ ሂዋርድ ሚልስ ስለ ትዳር ሰፋ ያለ ተጨባጭ ነገሮችን ያሳዩናል። ይህ ልዩ ምጽሐፍ ለአስተማሪውም ሆነ ለትዳር ጥንዶቸ ዝግጁ መገልገያ ነው። ትዳራችሁን የሚያሳምሩ እና የሚያስደስቱ ጠቋሚ ነገሮችን በእርግጥ ያገኙበታል። ይህ መጽሐፍ ከጋብቻ በፊት በትዳር ውስጥ እና ከትዳር በኋላ ላሉት ለሰው ልጆች ህብረት ውድ የሆኑ መሰረታዊ እና ተግባራዊ መረጃዎችን ያዘለ ነው። ስለ ወሲብ፤ ስለ ውልደት፤ ስል እርግዝና እና ልጅ ከመጣ በኋላ በሰው አካል አስተምሮ ላይ ተመርኩዞ በትልቅ ጥናት ተደርጎበት የተዘጋጀ ነው። የመጽሐፉ ዋነኛነት ውስብስብ ያለን መረጃ ቀላል እና ለመረዳት በሚያስችል መንገድ የዶክተር ዳግ ሂዋርድ ሚልስ አቀማመጥ ነው። በአጠቃላይ ሰለ ትዳር ገለጻ ፤ በጣም የጠለቅ፣ ለአጠቃቀም ቀላል በሆነ መንገድ የቀረበ መጽሐፍ ነው። ሰለ ጋብቻ ምክር የቢሾፕ ዳግ ሂዋርድ ሚልስ መጽሐፍ አቻ የልውም። የህክምና ዶክተር መሆኑ በግልጽ ያሳያችውና ያንጽባረቃችው፣ በተለይ በግል የህክምና አይኖቹ አገላልጽ የዚህን መጽሐፍ ልዩ መሆኑን ያንጽባርቃል። ኤድዊን ሞርጋን ኦጎ፣ የጋና የህክምና ዩኒቨርስቲ አስተማሪ

  • በእርግጥ እግዚአብሔር ብዙ ሰዎችን ጠርቷል፡፡ በእዚህ ምድር ላይ ያለን ሕይወት እግዚአብሔርን ለማገልገል የተሰጠን ዕድል ሲሆን የእርሱም ዓይኖች ለመንግሥቱ በምንሠራቸው ነገሮች ላይ ናቸው፡፡ ይህ መጽሐፍ ሲነበብ ያነቃቃል፡፡ በጸሐፊው የተላለፈውን መልእክት ብትቀበል፣ የሕይወትህን መልካም አጋጣሚዎች በአግባቡ እንድትጠቀምባቸው የሚረዳህን ጥበብ ትቀበላለህ፡፡

  • የቅባቱ ቦታው የተቀባው ሰው ጋር ነው። ቅባት ከተቀባው ሰው ጋር አይለያይም። ቅባቱ በእግዚአብሔር ሰው ውስጥ ነው! ቅባቱ ከእግዚአብሔር ሰው ጋር ነው! ቅባቱ በእግዚአብሔር ሰው ላይ ነው! ይህ በዳግ ሂዋርድ ሚልስ የተጻፈው ማራኪ አዲስ መጽሐፍ ቅባቱን ለሚፈልጉ ሁሉ ልባቸውን ቅባቱ ወዳለበት የሚጎትት ነው።

  • የቤተ ክርስቲያን እድገት አስቸጋሪና የማይጨበጥ እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ሁሉም መጋቢዎች ቤተ ክርስቲያኖቻቸው እንዲያድጉ ይፈልጋሉ፡፡ ይህ መጽሐፍ ስለ ቤተ ክርስቲያን እድገት ላለህ ጥያቄህ መልስ ይሆናል፡፡የቤተ ክርስቲያንን እድገት ለማየት እንዴት “ብዙ ነገሮች በአንድ ላይ እንደሚሰሩ " ትረዳለህ፡፡ ውድ መጋቢ፣ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉት ቃሎችና ቅባቱ በልብህ ውስጥ ሲገቡ፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን እድገት ትጸልይ የነበረውን በገሀድ ታየዋለህ፡፡

  • በህይወት ጉዞ ውስጥ ስትጓዝ የማይታየው አለም የእውነተኛው እንደሆነና ተፈጥሮዋዊው ደግሞ የማይታየው አለም መገለጥ እንደሆነ ግልጥ እያለ ይታወቅሃል። ግልጥ ያሉ ጠላቶች እንዳሉህ ሁሉ ድብቅ ጠላቶችም አሉህ። ጠላትህን ሳታውቀው፤ ስልቱን ሳትረዳ፤ አሰራሩን እና መሳሪያውን ሳታውቅ ልትዋጋው ትችላለህን? ለህይወትህ ጉዞ ይህ መጽሐፍ ዋነኛ ነው። በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የማይታየው ጠላትህ ማን እንደሆነ፤ የህልውናቸው ስር መሰረት፤ ባህሪያቸው እና እንዴት እንደምታሸንፋቸው ትማራለህ።ይህ ውድ መጽሐፍ የማይታዩትን ጠላቶችህን እንድትቋቋማቸው ይርዳህ!

  • በዚህ ዓይነተኛ መጽሐፍ ውስጥ፣ ቢሾፕ ዳግ ሂዋርድ-ሚልስ የታማኝነት መኖር የመሪውን ብቃት ምን ያህል እንደሚያዳብር ያስተምራሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን፣ የታሪክ እና የሥነ-ጽሑፍ ማጣቀሻዎችን መጠቀማቸው ደግሞ ርዕሰ ጉዳዩ ለማንኛውም ዓይነት መሪ ጠቃሚ እንዲሆን አድርጐታል፡፡

  • ታማኝነት ለመሪዎች የእግዚአብሔር የቅድሚያ መለኪያ ቢሆንም እንኳን ፣በእዚህ ርዕስ የተጻፉ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ዳግ ሂዋርድ ሚልስ በዚህ መጽሐፉ፣ የቤተክርስቲያኖች በመጽናት ማደግን አስመልክቶ በጣም አስፈላጊ መመሪያዎችን በግልፅ ይዘረዝርልናል፡፡ ይህ መጽሐፍ ወቅታዊና ተግባራዊ የሆኑ ርዕሶችን ያካተተ ነው ፣ በመሆኑም ለቤተክርስቲያን መሪዎች የሁልግዜ መገልገያ መሳሪያ ይሆናል፡፡

  • ይህ የሚበረታታ መጽሐፍ ነው፡፡ መጋቢ የሆነው ቢሾፕ ዳግ ሂዋርድ ሚልስ ለምንና እንዴት የመጋቢነትህን አገልግሎት ወጤታማ ማድረግ እንደሚቻል ያስረዳል።

  • እግዚአብሔርን መከተል አስደሳች የአዳዲስ ግኝት ጉዞ ነው፡፡ሌሎችን ሰዎች መከተልና መቅዳት ኢየሱስ ክርስቶስ ዋና የስልጠና ዘዴ አድርጎ የመረጣቸው ጥንታዊ የመማሪያ ጥበቦች ናቸው፡፡ከዚህ በጊዜ ከተፈተነ የስልጠና ዘዴ አፍሮ ከመሸሽ ይልቅ የመከተልን ጥበብ ውበትና ያለበትን ጭምትነት ለመረዳት ጊዜው አሁን ነው፡፡ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ማንን፣ ምንን እና እንዴት በሚገባ መከተል እንደሚገባህ ትማራለህ፡፡ይህ የዳግ ሂዋርድ ሚልስ ድንቅ መጽሐፍ ለመከተል ጥበብ በክርስትና ልምምዳችን ውስጥ ተገቢውን ቦታ ይሰጠዋል፡፡

Title

Go to Top