• መጽሐፍ ቅዱስ ሁላችንም እንደምናጠፋ ይነግረናል- መጋቢዎችም የተለዩ አይደሉም፡፡ ጥፋቶች ወደኋላ እንጂ ወደፊት እንድንራመድ አያደርጉንም ፡፡አንድም ጥፋት ከስኬትህ ሊያቆምህ ይችላል፡፡ አንድ መጋቢ ሊያጠፋ የሚችለው ነገር ምንድን ነው? የመጋቢዎች አሥሩ ዋና ዋና ስህተቶች ሊሆኑት የሚችሉት ነገሮች ምንድን ናቸው? አደጋ ሊሆኑብህ የሚችሉትን ስህተቶችን እራስህ እንድታይና አንድ መጋቢ ዋና ዋና የሚባሉትን ስህተቶች ከማድረጉ በፊት እንዴት ማስወገድ እንዳለበት የዚህን ድንቅ መጽሐፍ ገፆች እየገለጥክ እንድታነብ ተጋብዘሃል፡፡

  • አብያተ ክርስቲያናት ፍጹም ታማኝ ወዳለመሆን ደረጃ በሚደርሱ ፍጹም አስመሳዮች ተሞልታለች፡፡ ሁል ጊዜም የሰይጣን ዋንኞቹ ቁልፎች ማሳት እና ማስመሰል ናቸው፡፡ አስመሳይ ከሚያደርገው የማስመሰል ጭንብል በስተጀርባ አልፎ ማይት የማይችል መሪ፣ አለማየት ካለመቻሉ የተነሳ ይሰቃያል፡፡ ማስፈራራት፣ መላመድ፣ ግራ መጋባት አገልጋዮችን የሚዋጉ ክፉ መናፍስት ናቸው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ፣ ሰዎች ምን እየተዋጋቸው እንዳለ እንኳን አያውቁም፡፡ ይህ መጽሐፍ ይህንን ለይተህ እንድታውቅና ከውስጥ ያሉትን ጠላቶችህን እንድትዋጋ ይረዳሃል፡፡

  • የቅድመ-ውሳኔ (Predestination) ጉዳይ በጣም አጓጊ ርዕስ ነው፤ ምክንያቱም ነገሮች አስቀድመው እንደሚወሰኑ የሚያሳዩ ግልጽ ማስረጃዎች በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ይገኛሉ። በቅድመ-ውሳኔ ማመን ማለት፣ ማንም ሰው በክስተቶች ላይ እውነተኛ ቁጥጥር እንደሌለውና ይልቁንም ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ዕቅድና ዓላማ አስቀድሞ እንደተወሰነ ማመን ማለት ነው። በሌላ በኩል ደግሞ፣ እግዚአብሔር ነፃ ፈቃድ እንደሰጠንና በብዙ ነገሮች ላይ እኛ እንድንወስን እንደሚጠብቅብን የሚያሳዩ ማስረጃዎች አሉ። እግዚአብሔር በመልካምና በክፉ መካከል የመምረጥ ነፃነት ሰጥቶናል። ሁኔታዎች ከሚከናወኑበት መንገድ አንጻር የቅድመ-ውሳኔ ጽንሰ-ሐሳብን ለመረዳት አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ቅድመ-ውሳኔ እውነት ነው! ከእግዚአብሔር ጋር በበለጠ ቅልጥፍና ለመስራትና ለመራመድ እንድትችሉ ቅድመ-ውሳኔን የምትረዱበት ጊዜ አሁን ነው። ይህ በታዋቂው ደራሲ ዳግ ሂዋርድ-ሚልስ (Dag Heward-Mills) የቀረበ ሌላ አሳሳቢና ድንቅ መጽሐፍ ነው። በእግዚአብሔር ይታመኑ፤ እግዚአብሔር ለእርስዎ የወሰናቸው (destined) ነገሮች ሁሉ እንዴት እንደሚገለጡም ይመልከቱ።
  • እግዚአብሔር ብዙ ችሎታዎችን ሰጥቶዎታል። የእግዚአብሔር ስጦታ በውስጥዎ አለ! ይህ ስጦታ በውስጥዎ ሳይሠራበትና ተኝቶ እንዲቀር አይፍቀዱ። ዓለም እነዚህ ስጦታዎች በእርስዎ ውስጥ ተገልጠው እስኪታዩ እየተጠባበቀ መሆኑን ያስታውሱ። በውስጥዎ ያሉትን እነዚህን ስጦታዎች ማንቀሳቀስና እንዲገለጡ ማድረግ ይኖርብዎታል። ብዙ ሰዎች ይድናሉ! የእግዚአብሔር ስጦታ በእርስዎ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ተቀስቅሶ ወደ ተግባር ሲገባ ብዙ ሰዎች ይፈወሳሉ፣ ብዙዎችም ይባረካሉ! በዙሪያዎም እንዲሁ ብዙ ተሰጥኦ ያላቸው ሰዎች አሉ። እንደ አለመታደል ሆኖ ብዙዎቹ ስጦታቸውን ሳይጠቀሙበት ወይም ምን ማድረግ እንደሚችሉ ሳያሳዩ ይኖራሉ፣ ይሞታሉም። ብዙ ተሰጥኦ ያላቸው ሰዎች ስጦታቸውን ሳይቀሰቅሱ ሕይወታቸውን ይገፋሉ። የእነርሱን ስጦታ ካነቃቁት በዙሪያዎ እጅግ የተዋጣላቸው ሰዎች እንዳሉ ይረዳሉ። ይህ ውድ መጽሐፍ የእርስዎንና በዙሪያዎ ያሉትን ሰዎች ስጦታ እንዴት ማንቃት እንደሚችሉ የሚያስተምር ነው። በደራሲውና በፓስተሩ ዳግ ሂዋርድ-ሚልስ የተዘጋጀውን ይህን ጥልቅ ሥራ ካነበቡ በኋላ ለዓለም አስገራሚ ሰው ይሆናሉ! ብዙዎች በእርስዎ ውስጥ ባለው የእግዚአብሔር ስጦታ ታላቅነት ይደነቃሉ። እርስዎ የተቀቡ ነዎት! በእግዚአብሔር የተጠሩ ነዎት! የእግዚአብሔር ስጦታ አለዎት! ብዙ ነገሮች በውስጥዎ ተኝተው ይገኛሉ። ዓለም የመንፈስ ቅዱስን ኃይል እንዲገልጡ ይጠብቅዎታል። የእግዚአብሔርን ስጦታ ያንቁ!
  • የወንጌል ስርጭትን ተቃዋሚዎች፣ ምክንያቶች፣ ጥርጣሬና ተናዳጆች ባሉበት ቦታ ሁሉ ውጤታማና ፍሬያማ የሚያደርገውን የዚህን የግድማለት ኃይል ተማረው። የዚህ የዳግ ሂዋርድ ሚልስ መጽሐፍ ከዚህ በፊት ካደረከው በላይ ሰፍሳትን የምታድን ያደርግሃል።

  • ይህ መጽሐፍ ሊያነቡት ግድ ለሚላቸው አገልጋዮች ሁሉ ከዳግ ሂዋርድ-ሚልስ የተገኘ ሌላ ስጦታ ነው፡፡ ይህ መጽሐፍ በአባትና በልጅ መካከል ያሉትን ውስብስብ ግንኙነቶች ስለመወጣት ያሉ ጥያቄዎችን ይመልሳል፡፡ በዚህ መጽሐፍ ትምህርት አማካኝነት እርግማንን ከሕይወትህ አርቀህ በራስህ ላይ በረከትን ታመጣለህ አባቶች መርገምን ከሕይወትህ አርቀህ በረከትን በራስህ ላይ ታመጣለህ፡፡ አባቶች ልጆችንና ተከታዮችን የሚያሳድጉ ልዩ ስዎች ናቸው፡፡ ያለ አባቶች አገልግሎቱን ወደሌላ ትውልድ የሚያሸጋግሩ ልጆች አይኖሩም፡፡ ከአባቶች ጋር ለመቆራኘት ባለህ ችሎታ መሠረት የእግዚአብሔር ጥሪ ወይ ያብባል ወይ ይሞታል፡፡ ይህንን መጽሐፍ በማንበብ

  • መለኮታዊ ኃይል ዛሬም አለን ? በመለኮታው ኃይል ውስጥ ሆኜ ማገልገል እችላለሁን ? እግዚአብሔር አሁንም ሰዎችን እየፈወሰ ከሆን ፣ለምን ሁሉንም አይፈውስም ? የፈውስን ቅባት እንዴት ልቀበል እችላለሁ ? በዚህ ድንቅ የዳግ ሂዋርድ ሚልስ መጽሐፍ የተለያዩ ገፆች ውስጥ ለእነዚህና ለሌላም ብዙ ጠያቄዎችህ መልሶቹን ድረስባቸው።

  • በዚህ ዓይነተኛ አዲስ የዳግ ሂዋርድ-ሚልስ መጽሐፍ ውስጥ የአጋንንቶች አሠራር ተጋልጧል፡፡ የጌርጌሴኖኑ በርኲስ መናፍስት ተይዞ የነበረ ሰው ምስክርነት በመጠቀም፣ በአጋንንቶች እና ርኲስ መናፍስት ላይ ድል የሚገኝበትን መንገድ ያሳያል፡፡

  • እረኛ የሚለውን ቃል ስንሰማ በሃሳባችን የሚመጣው « በግ « ነው። በጎች በእረኞች የሚያስፈልጋቸው ጥገኛ የሆኑ ፍጡሮች ናቸው። እረኛ በጎችን የሚንከባከብና የሚወድ እነርሱንም የሚመራ ነው። በመጽሐፍ ቅዱስ እግዚአብሔር እኛ የእርሱ የማሰማርያው በጎችን እንደሆንን ያሳየናል። ኢየሱስ ደቀመዝሙሩን ጴጥሮስን ለጌታ ፍቅር ማረጋገጫ እንዲሆን በጎቼን መግብልኝ ብሎታል። እረኛ መሆን ትልቅ ሥራ ነው። በእግዚአብሔር ግብረኃይል ውስጥ በመካተት በጎችን መጠበቅ ትልቅ መታደል ነው። በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ዳግ ሂዋርድ ሚልስ የእግዚአብሔርን ህዝብ የመጠበቅ ታላቅ ሥራ ውስጥ እንዴት አድርገን መግባት እንዳለብን ይጋብዘናል፣ይገፋፋናል፣ያሳየናል። ካማረው

  • የማይጠማውን ሰው እንዲጠጣ ማድረግ በጣም አስቸጋሪ ነው ። መጠጣት እንዲችል ጥማት መኖር አለበት ። እስከ ሞት ድረስ የታመነ መሆን ማለት በሕይወትህ ዘመን ሁሉ ተስፋ አለመቁረጥ ማለት ነው! እስከ ሞት ድረስ የታመነ መሆን ማለት እስከ ሞት ድረስ ታማኝ፣ ጽኑ፣ ያው፣ የማይናወጥና የማይለወጥ መሆን ማለት ነው ። ጌታን በማገልገልህ ስትቀጥል፣ በእርግጥ መሰናከል፣ መውደቅና አለመታመን የሚያጋጥሙህ አጋጣሚዎች ይመጣሉ ። ኢየሱስ በማቴዎስ 18:7 ላይ እንዲህ ሲል ያስጠነቅቀናል፦ “...መሰናክል ሳይመጣ አይቀርምና፤...” ብዙ ሰዎች ሩጫቸውን ይሮጣሉ፤ ነገር ግን በአንድ ወይም በሌላ ምክንያት በድንገት ወድቀው መሬት ላይ የሚፈጥጡበት ደረጃ ላይ ይደርሳሉ ። የመሰናከያ ድንጋዮች ወደሚጠበቀው ፍጻሜ መድረስን የማይቻል ሊያደርጉት ይችላሉ ። አንተም መከላከል ያለብህ ይህንን ነው! መሬት ላይ እንዳትወድቅና ከሩጫው ውጭ እንዳትሆን ተጠንቀቅ ። እነዚህ የአዳኛችን መመዘኛዎች ናቸው፤ በእነርሱም ማመንህና በተግባር ላይ ማዋልህ አስፈላጊ ነው ። በታዋቂው ደራሲ ዳግ ሂዋርድ-ሚልስ የተጻፈው ይህ ወቅታዊ መጽሐፍ እስከ መጨረሻው ድረስ በታማኝነት እንድትጸና ያነቃቃሃል ።
  • እግዚአብሔር የሰጠውን ተሰጥኦ ለመንግሥቱ የማይጠቀም ማንኛውም ሰው፣ ጣዕሙን እንዳጣ ጨው ነው። ፍሬ አልባ አገልጋዮች ጣዕሙን ላጣ ጨው ጥሩ ምሳሌዎች ናቸው። ኢየሱስም የማይጠቅም አገልጋይ ለምንም እንደማይረባ ተናግሯል። ጨው መኖሩ እንዲታወቅ ማድረግ አስፈላጊ ነው። በምግብህ ውስጥ ጨው ሊኖር ይችላል፤ ነገር ግን ተፅዕኖ እንዲኖረው በቂ መሆን አለበት። እናንተ የምድር ጨው ናችሁ፣ ስለዚህ በዚህች ምድር ላይ መኖራችሁ እንዲታወቅ ማድረግ አለባችሁ! ለመንግሥቱ ለምንም የማትረቡ ናችሁ? ስለ ጨውና ስለ ምስጢራዊ ተፅዕኖው እንዲሁም ለእግዚአብሔር መንግሥት ስላለው ትንቢታዊ ጠቀሜታ የሚናገረው ይህ የትንቢት መጽሐፍ፣ ለእግዚአብሔር ስላላችሁ ጠቃሚነት ወይም ጥቅም አልባነት በጥልቀት እንድታሰላስሉ ያደርጋችኋል። በሕይወታችን ውስጥ ያለውን የጨው ሚና በመመርመርና በመረዳት፣ ለምንም የማይረባ መሆን ምን ማለት እንደሆነ በዚህ ቀስቃሽ መጽሐፍ ውስጥ ትማራላችሁ። ለምንም የማትረቡ አያድርጋችሁ!
  • ኢየሱስ ሲናገር፡- እንደ እባብ ልባሞች እንደ ርግብም የዋሆች ሁኑ። በእውነትም እባቦች ልባሞች ናቸውን? ኢየሱስ ለምንድን እንደዚህ ያለ ምክር ሰጠ? ግልጥ አድርጎ የሚያስረዳውን የዳግ ሂዋርድ ሚልስን መጽሐፍ ያዝና ድብቅ የሆኑትን የእባብ ብልሀቶች ተማ

Title

Go to Top