• በዚህ ዓይነተኛ መጽሐፍ ውስጥ፣ ቢሾፕ ዳግ ሂዋርድ-ሚልስ የታማኝነት መኖር የመሪውን ብቃት ምን ያህል እንደሚያዳብር ያስተምራሉ፡፡ መጽሐፍ ቅዱስን፣ የታሪክ እና የሥነ-ጽሑፍ ማጣቀሻዎችን መጠቀማቸው ደግሞ ርዕሰ ጉዳዩ ለማንኛውም ዓይነት መሪ ጠቃሚ እንዲሆን አድርጐታል፡፡

  • በህይወት ጉዞ ውስጥ ስትጓዝ የማይታየው አለም የእውነተኛው እንደሆነና ተፈጥሮዋዊው ደግሞ የማይታየው አለም መገለጥ እንደሆነ ግልጥ እያለ ይታወቅሃል። ግልጥ ያሉ ጠላቶች እንዳሉህ ሁሉ ድብቅ ጠላቶችም አሉህ። ጠላትህን ሳታውቀው፤ ስልቱን ሳትረዳ፤ አሰራሩን እና መሳሪያውን ሳታውቅ ልትዋጋው ትችላለህን? ለህይወትህ ጉዞ ይህ መጽሐፍ ዋነኛ ነው። በዚህ መጽሐፍ ውስጥ የማይታየው ጠላትህ ማን እንደሆነ፤ የህልውናቸው ስር መሰረት፤ ባህሪያቸው እና እንዴት እንደምታሸንፋቸው ትማራለህ።ይህ ውድ መጽሐፍ የማይታዩትን ጠላቶችህን እንድትቋቋማቸው ይርዳህ!

  • የቤተ ክርስቲያን እድገት አስቸጋሪና የማይጨበጥ እንደሆነ እናውቃለን፡፡ ሁሉም መጋቢዎች ቤተ ክርስቲያኖቻቸው እንዲያድጉ ይፈልጋሉ፡፡ ይህ መጽሐፍ ስለ ቤተ ክርስቲያን እድገት ላለህ ጥያቄህ መልስ ይሆናል፡፡የቤተ ክርስቲያንን እድገት ለማየት እንዴት “ብዙ ነገሮች በአንድ ላይ እንደሚሰሩ " ትረዳለህ፡፡ ውድ መጋቢ፣ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ያሉት ቃሎችና ቅባቱ በልብህ ውስጥ ሲገቡ፣ ስለ ቤተ ክርስቲያን እድገት ትጸልይ የነበረውን በገሀድ ታየዋለህ፡፡

  • እግዚአብሔር ትዕግሥት እንደሚያስፈልገው የሚናገረው ማንኛውም ነገር “የትዕግሥቴ ቃል” ነው። አብዛኞቹ የእግዚአብሔር ተስፋዎች “የትዕግሥቴ ቃል” ምሳሌዎች ናቸው። እግዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ነገሮችን ተስፋ ይሰጣል፣ ነገር ግን አብዛኞቹ ተስፋዎች ሲፈጸሙ ለማየት ትዕግሥት ያስፈልጋቸዋል። “የትዕግሥቴ ቃል” ማለት ብዙ መቆጣትን፣ መበሳጨትን ወይም ሥቃይን ያለ ቅሬታ እንድትታገሥ የሚፈልግ ቃል ነው። “የትዕግሥቴ ቃል” ግልፍተኝነት ሳይሰማህ ወይም ሳትበሳጭ ፈተናዎችን፣ መከራዎችንና መጥፎ ዕድሎችን እንድትቋቋም የሚፈልግ ቃል ነው። የእግዚአብሔር ተስፋ በሕይወትህ ተገልጦ ለማየት ከፈለግህ “የትዕግሥቴ ቃል” የማያወለዳዳና ዝምተኛ ጽናት እንዲሁም ትጋት ይጠይቃል። እንደገናም ቢሾፕ ዳግ ሂዋርድ-ሚልስ፣ በዚህ ማብራሪያው የእግዚአብሔርን ተስፋ ለመቀበል ሲሉ “የትዕግሥቴን ቃል” መታገሥ የነበረባቸውን በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ያሉ ታላላቅ ሰዎችን ተሞክሮ በጥንቃቄ ይዘረዝራል። ውድ ወዳጄ ሆይ፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ በመፈጸም እና “የትዕግሥቴን ቃል” ለመለማመድ ወደፊት በመገስገስ ሂደት ውስጥ፣ የተስፋዎቹን ፍጻሜ በሕይወትህ ለማየት ብዙ ነገሮችን በረጋ መንፈስ፣ በትዕግሥትና በጽናት መቀበል እንዳለብህ ማመን አለብህ።
  • የቅባቱ ቦታው የተቀባው ሰው ጋር ነው። ቅባት ከተቀባው ሰው ጋር አይለያይም። ቅባቱ በእግዚአብሔር ሰው ውስጥ ነው! ቅባቱ ከእግዚአብሔር ሰው ጋር ነው! ቅባቱ በእግዚአብሔር ሰው ላይ ነው! ይህ በዳግ ሂዋርድ ሚልስ የተጻፈው ማራኪ አዲስ መጽሐፍ ቅባቱን ለሚፈልጉ ሁሉ ልባቸውን ቅባቱ ወዳለበት የሚጎትት ነው።

  • በእርግጥ እግዚአብሔር ብዙ ሰዎችን ጠርቷል፡፡ በእዚህ ምድር ላይ ያለን ሕይወት እግዚአብሔርን ለማገልገል የተሰጠን ዕድል ሲሆን የእርሱም ዓይኖች ለመንግሥቱ በምንሠራቸው ነገሮች ላይ ናቸው፡፡ ይህ መጽሐፍ ሲነበብ ያነቃቃል፡፡ በጸሐፊው የተላለፈውን መልእክት ብትቀበል፣ የሕይወትህን መልካም አጋጣሚዎች በአግባቡ እንድትጠቀምባቸው የሚረዳህን ጥበብ ትቀበላለህ፡፡

  • እግዚአብሔር ትዕግሥት ይጠይቃል የሚለው ማንኛውም ነገር "የትዕግሥቴ ቃል" ነው። አብዛኞቹ የእግዚአብሔር ተስፋዎች "የትዕግሥቴ ቃል" ምሳሌዎች ናቸው። እግዚአብሔር በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ተስፋዎችን ሰጥቷል፣ ነገር ግን አብዛኞቹ እነዚህ ተስፋዎች ሲፈጸሙ ለማየት ትዕግሥት ያስፈልጋል። "የትዕግሥቴ ቃል" ማለት ብዙ ትንኮሳን፣ መበሳጨትን ወይም ሥቃይን ያለ ቅሬታ እንድትቋቋሙ የሚጠይቅ ቃል ነው። "የትዕግሥቴ ቃል" ማለት ቁጣን ሳያወጡ ወይም ሳይበሳጩ ፈተናዎችንና መከራዎችን እንድትቋቋሙ የሚጠይቅ ቃል ነው። የእግዚአብሔር ተስፋ ሲገለጥ ለማየት ከፈለጉ "የትዕግሥቴ ቃል" ጽኑና ዝምተኛ ጽናት እንዲሁም ትጋትን ይጠይቃል። በዚህ ጥናት ውስጥ ቢሾፕ ዳግ ሂዋርድ-ሚልስ፣ የእግዚአብሔርን ተስፋ ለመቀበል ሲሉ "የትዕግሥቴን ቃል" መታገሥ የነበረባቸውን የታላላቅ የመጽሐፍ ቅዱስ ሰዎችን ልምድ በዝርዝር ያሳያል። ውድ ጓደኛዬ፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመፈጸም እና "የትዕግሥቴን ቃል" ለመለማመድ ወደፊት ስትገፋ፣ በሕይወትህ ውስጥ የእርሱ ተስፋዎች ሲፈጸሙ ለማየት በረጋ መንፈስ፣ በትዕግሥትና በጽናት ማለፍ ያለብህን ብዙ ነገሮችን መቀበል አለብህ።
  • በዚህ ለየት ባለ መጽሐፍ ውስጥ ዳግ ሂዋርድ ሚልስ ስለ ትዳር ሰፋ ያለ ተጨባጭ ነገሮችን ያሳዩናል። ይህ ልዩ ምጽሐፍ ለአስተማሪውም ሆነ ለትዳር ጥንዶቸ ዝግጁ መገልገያ ነው። ትዳራችሁን የሚያሳምሩ እና የሚያስደስቱ ጠቋሚ ነገሮችን በእርግጥ ያገኙበታል። ይህ መጽሐፍ ከጋብቻ በፊት በትዳር ውስጥ እና ከትዳር በኋላ ላሉት ለሰው ልጆች ህብረት ውድ የሆኑ መሰረታዊ እና ተግባራዊ መረጃዎችን ያዘለ ነው። ስለ ወሲብ፤ ስለ ውልደት፤ ስል እርግዝና እና ልጅ ከመጣ በኋላ በሰው አካል አስተምሮ ላይ ተመርኩዞ በትልቅ ጥናት ተደርጎበት የተዘጋጀ ነው። የመጽሐፉ ዋነኛነት ውስብስብ ያለን መረጃ ቀላል እና ለመረዳት በሚያስችል መንገድ የዶክተር ዳግ ሂዋርድ ሚልስ አቀማመጥ ነው። በአጠቃላይ ሰለ ትዳር ገለጻ ፤ በጣም የጠለቅ፣ ለአጠቃቀም ቀላል በሆነ መንገድ የቀረበ መጽሐፍ ነው። ሰለ ጋብቻ ምክር የቢሾፕ ዳግ ሂዋርድ ሚልስ መጽሐፍ አቻ የልውም። የህክምና ዶክተር መሆኑ በግልጽ ያሳያችውና ያንጽባረቃችው፣ በተለይ በግል የህክምና አይኖቹ አገላልጽ የዚህን መጽሐፍ ልዩ መሆኑን ያንጽባርቃል። ኤድዊን ሞርጋን ኦጎ፣ የጋና የህክምና ዩኒቨርስቲ አስተማሪ

  • ከብዙ የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀት የምስክር ወረቀቶች ክምችት በላይ ለአገልግሎት የሚያስፈልግ ሌላ ነገር አለ። መካንነት (Barrenness) በተፈጥሮም ሆነ በአገልግሎት ውስጥ የሚከሰት አስከፊ፣ አስጨናቂ እና አውዳሚ ችግር ነው። በአገልግሎት ውስጥ የሚታይ መካንነት ለብዙዎቻችን መጋቢዎች (pastors) ተስፋ መቁረጥ፣ ቅሬታ እና ግራ መጋባት ምክንያት ነው። ብዙ መጋቢዎች በአገልግሎታቸው መካን ስለሆኑ በተስፋ መቁረጥ እና በግራ መጋባት ምክንያት ከሩጫው ይወጣሉ። በዘመናዊቷ የክርስቲያን ቤተክርስቲያን ውስጥ እውነተኛ ፍሬ ለማጣት ምክንያቱ መካንነት ነው። ብዙ እንቅስቃሴዎች እና ብዙ ፕሮግራሞች አሉ፤ ነገር ግን ፍሬው ጥቂት ነው ወይም ጨርሶ የለም። እግዚአብሔር ፍሬያማ እንድንሆን ይፈልጋል። እግዚአብሔር በአገልግሎት እንድንሰፋ ይፈልጋል። ፍሬያማ ለመሆን መካንነት በትክክል ምን እንደሆነ መረዳት አለብዎት። መካንነት እግዚአብሔር በአገልግሎትዎ ውስጥ ሊፈታው የሚፈልገው ችግር ነው። በዳግ ሂዋርድ-ሚልስ (Dag Heward-Mills) የተዘጋጀው ይህ ወቅታዊ መጽሐፍ፣ በአገልግሎትዎ ውስጥ ካለ መካንነት እንዲወጡ ይረዳዎታል። የመካንነት መንፈስ ሲወገድ፣ ወደ ፍሬያማነት ይሸጋገራሉ። ዛሬ ከመካንነት እየወጡ ነው!
  • ዳግ ሂዋርድ ሚልስ በጊዜው አገልግሎት ውስጥ ያለውን የእውነተኛ ህይወት ገጠመኞች በዚህ ድንቅ ስራው ይገመግማል፡፡ ገንዘብ፣ፖለቲካ፣ከተቃራኒ ፆታ ጋር ስለሚኖረን ግንኙነቶችና አገልግሎታዊ ተጽዕኖችን የመሳሰሉትን ጠቃሚ የሆኑ ጉዳዮችን ያሳየናል፡፡ ይህ መጽሐፍ ለእያንዳዱ መሪ ሊኖረው የሚገባ፣ ለጥሪህ መሰረታው የሆኑ ልምምዶችን በቀላሉ የሚያስረዳ መመሪያ ነው፡፡ ለመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና በቤተክርስቲያን ውስጥ ለሚሰሩ እንዲኖራቸው በከፍተኛው የሚመከር ነው።

  • ጥበብን ማዳበር ችሎታን ወይንም ክህሎትን ማዳበር ማለት ነው። መጽሐፍ ቅዱስ ሲናገር ሞገስ አዋቂ ለሆኑት ትመጣለች ይላል። የአገልግሎትም ሥራ ትልቅ ችሎታን ይጠይቃል። ይህ « የአገልግሎት ጥበብ » በመባል የወጣው አዲስ መጽሐፍ የአገልግሎትን ሥራ መስራት ለሚፈልጉ በጣም አስፈላጊ ነው። ስለ አገልግሎት ትክክለኛና ትክክል ያልሆነ አስተሳሰብ ምን እንደሆነ፣የአገልግሎት ሥራ ምንድን ነው፣ በአገልግሎቱ ሥራ ውስጥ ካንተ የሚጠበቀው ምንድን ነው እና የአገልጋይነቴን ተግባር እንዴት ነው የምወጣው የሚሉትን በማብራራት በግልጽ ያስቀምጠዋል። በአገልግሎት ውስጥ ያንተን ተግባር እንዴት መሥራት እንዳለብህ ያሳስብሃልን? ይህ ልዩ የሆነ የዳግ ሂዋ

  • ማናችንም በምድር የተሰጠንን ስራ ሳንጨርሰ በሰማዩ ቤታችን መግባት አንፈልግም። አንዳችንም ስንኳ!እግዚአብሔር ለኛ የሰጠንን ስራ መጨረስ እንፈልጋለን። ይህ መጽሐፍ እንዴት ማጠናቀቅ እንደምትችል ይነግርሃል። ይህ መጽሐፍ በዚያ ቀን ምንም አልጎድለኝም እንዳትል በህይወትህ ውስጥ ለሚያጋጥሙህ መለኮታዊ ወቅቶች እንዴት መመለስ እንዳለብህ ያሳይሃል። ስራህን አጠናቅቀህ እግዚአብሔር “ አንተ በጎ ታማኝ ባሪያ” ለመባል ያብቃህ!

Title

Go to Top